ሰበር ዜና- ፍትህ ጋዜጣ እንዳይሰራጭ ታገደች!

ሰበር ዜና-
ፍትህ ጋዜጣ እንዳይሰራጭ ታገደች!
በትላ ንትናው ዕለት ለስርጭት መብቃት የነበረባት ፍትህ የጠቅላይ ሚንስትሩን መታተም ተከትሎ በተፈጠረው የስልጣን ትግል እያሸነፈ በመጣው አክራሪ ሀይል ተስተጓጉላ የነበረ ቢሆንም በማግስቱ እንድትታተም ተፈቅዷል ተብሎ ታተመች፡፡ ትላንት ከምሽቱ 2 ሰዓት ላይም ሙሉ በሙሉ ታትማም አለቀች፡፡ ነገር ግን አንባቢያን እጅ ልትደርስ አልቻለችም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ (በዛው ኃይል ትዕዛዛ ይመስለኛል) በአቃቢ ህግ ብርሃኑ ወንድምአገኝ ‹‹ለሀገር ደህንንት የሚያሰጋ ዘገባ በጋዜጣው ላይ መታተሙ መረጃ ስለደረሰን እንዲታገድ ወስነናል›› በሚል የተፈረመ የዕግድ ደብዳቤ ማተሚያ ቤቱ እንደደረሰው ገለፀልን፡፡ በዚህም ምክንያት በአሁኑ ሰዓት 30 ሺህ የፍትህ ጋዜጣ እትም በብርሃና ሰላም ማተሚያ ቤት ተቆልፎበት ይገኛል፡፡
…እንዴት ነው ነገሩ? ‹‹ትሻልን ፈትቼ ትብስን አገባሁ›› እየሆነ ነው? ይህ ሁኔታ ወደስልጣን እየመጣ ያለው ሀይል የባሰ እንደሆነ ምልክት እያሳየስ ይሆን? ለማንኛውም መጨረሻውን አይተን የራሳችንን እርምጃ እንወስዳለን፡፡
(ማተሚያ ቤቱ ለጋዜጣው ዝግጅት ክፍል የላከውን ደብዳቤ ከስር ይመልከቱ)

የጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲስ አበባ መግባት እና የፖለቲካው አሰላለፍ

በተመስገን ደሳለኝ
የአቶ መለስን መታመም ተከትሎ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ አራት ሀይሎች ‹‹በሸዋ ፖለቲካ›› ጥበብ ግብግብ ገጥመዋል። በእርግጥ አንደኛው ሀይል (ቡድን አንድ) የበላይ የመሆን ዕድሉን እያሰፋ ነው።
(እኔ ካገኘሁት መረጃ አንፃር አሸናፊው ቡድን እንዲህ አይነት ገፅታ ሊኖረው ይችላል፡፡ አቀራረቤም በአገኘሁት መረጃ ላይ ተንተርሼ ለመተንተን የሞከርኩት ነው፡፡

Pages