አንገት ሲደፋ ምን ፈሰሰ?

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም
ሰሞኑን አዲስ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፎቶግራፍ በብዛት በያለበት ይታይ ነበር፤ ያዘነ፣ የተከዘና አንገቱን የደፋ መለስ ዜናዊ! እኔን ቀልቤን የሳበው የጠቅላይ ሚኒስትሩን አንገት ሊያስደፋ የቻለው ነገር አይደለም፤ ወይም አበበ ገላው የተናገረው ነገር አይደለም፤ አበበ ገላው የተናገረውን ለመናገር ሙሉ መብት አለው፤ በተባለው ነገር የማይስማማ ሰው በማስረጃም ሆነ ያለማስረጃ የተባለውን ለማስተባበል መሞከር መብቱ ነው፤ የአሜሪካኑን ፕሬዚዳንት፣ ወይም የእንግሊዙን ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲህ ያለ ሁኔታ ቢያጋጥማቸው፣ ወይም በጆርጅ ቡሽ ላይ አንዱ ኢራቃዊ እንዳደረገው ጫማውን እያወለቀ ቢወረውርም ምንም የሚያስደንቅ ነገር አይኖርም፤ በ1928 ነው 29 አጼ ኃይለ ሥላሴ በቀድሞ የዓለም መንግሥታት ማኅበር መድረክ ላይ ሲናገሩ የኢጣሊያ ፋሺስቶች ያሰማሩአቸው ሰዎች ንግግሩን ለማደናቀፍ ጩኸትና ፉጨት ያሰሙ ነበረ፤ አጼ ኃይለ ሥላሴን አንገታቸውን አላስደፋቸውም፤ አበበ ገላው የወረወራቸው ቃላት ናቸው፤ ቃላቱ እውነትን የሚገልጹ ከሆነ በተግባራዊ ማረሚያ ይለወጣሉ፤ ቃላቱ ሐሰትን የሚገልጹ ከሆኑ እውነትን በሚገልጹ ቃላት ይደመሰሳሉ።
እዚህ ላይ አንድ ሌላ ነገር እናስታውስ፤ በመስከረም ግድም ይመስለኛል አቶ ኢሳይያስ አፈወርቅ በኒውዮርክ ነበረ፤ በዚያን ጊዜ በአንድ ስቴድየም ውስጥ የኤርትራ ተወላጆች ሁሉ (የቀረም ያለ አይመስልም!) በስቴድየሙ ታምቀው የኢሳያስን ዲስኩር ከሰሙ በኋላ አስተያየታቸውን እየሰጡና ጥያቄያቸውንም እየጠየቁ ሲወያዩ ነበር፤ ያስቀኑ ነበር፤ የኤርትራም ማኅበረሰብ እንደኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ውስብስብና ጉራማይሌ ነው፤ መሪው ህዝቡን ሳይፈራ፤ ሕዝቡም መሪን ሳይፈራ ተቀራርበው ለመወያየት መቻላቸው እኛን የትና የት ጥለውን እንደሄዱ አያሳይም የሚል አለ? ይህንን እውነት ቢያንስ የዛሬ አሥራ አምስት ዓመት ግድም ሪፖርተር የመጀመሪያውን መጽሔት ባወጣ ጊዜ ሽፋኑ የኢሳይያስ አፈወርቅ ፎቶግራፍ ነበር፤ የመለስ አልነበረም፤ ለኢሳይያስም ከተደረደሩት የውዳሴ ርእሶች አንዱ ኢሳይያስ ለሕዝብ ቅርብ መሆኑ ነበር፤ በአንፃራዊ ዝምታ መለስን ይጎሽም ነበር፤ ዛሬ በጠብ ላይ በመሆናችን እውነትን የምናይበት ዓይናችን ተቸግሮ ይሆናል፤ ለማናቸውም የሪፖርተርን ዘገባ ያስታወስሁት በኒውዮርክ በተደረገው የኤርትራ ተወላጆች ስብሰባ የተነሣ ነው፤ ለመሆኑ በኒውዮርክ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስተር ስብሰባ ቢጠራ መጀመሪያ ስንት ሰዎች ይገኛሉ? ከተገኙትስ ጋር የሠለጠነ ውይይት ይደረጋል? ወይስ በፓርላማ እንደተለመደው ያለ ይሆናል? ሳይናናቁ መሪና ሕዝብ ተከባብረው በነፃነት ሀሳባቸውን መለዋወጥ መቻል ትልቅ እርምጃ ነው።
በኒውዮርክ የተሰበሰቡትን የኤርትራ ተወላጆች ቁጥር የሚያህል ኢትዮጵያውያን ተሰብስበው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር መወያየት የሚችሉ ቢሆን እንዴት ያኮራኝ ነበር፤ በበኩሌ ባንስማማም እንነጋገር እያልሁ ስጮህ ብዙ ጊዜ ሆነኝ፤ ክርር ምርር ብሎ ከዚህ ፍንክች አልልም፤ ለአጭሩም፣ ለረጅሙም፣ ለወፍራሙም፣ ለቀጭኑም፣ ለክርስቲያኑም ለእስላሙም፣ ለሁላችሁም የሚበጀውን እኔ አውቃለሁ ማለቱ አያቀራርበንም፤ መናናቅ አያቀራርበንም፤ መፈራራት አያቀራርበንም፤ አበበ ገላው የተናገረው እውነት መሆኑንና አለመሆኑን ወደጎን እንተወውና በኢትዮጵያ ውስጥ እነዚያኑ ቃላት፣ በዚያው የጋለ ስሜት ያለፍርሃት በልበ ሙሉነት መግለጽ የሚቻል ቢሆን የአሜሪካው ድራማ አያስፈልግም ነበር፤ ዋጋም የሚሰጠው አይሆንም ነበር፤ በአሜሪካ በድንገትና ዓለም ሁሉ በሚያይበት መድረክ ስለ መለስ ዜናዊ የተባለው ሁሉ በኢትዮጵያ ውስጥ ተዝናንቶና ኮርቶ ሊያዳምጥ የሚችልበትን መድረክ በሃያ ዓመታት ውስጥ ሳያዘጋጅ መቅረቱ አንገቱን ለማስደፋቱ አስተዋጽኦ አድርጓል።
በኢትዮጵያ ሳይሆን በአሜሪካ፣ በኢትዮጵያ ፓርላማ ሳይሆን በትልቅ ዓለም-አቀፍ ስብሰባ፣ ጥቂት የአፍሪካ መሪዎች ብቻ በተጋበዙበት ስብሰባ፣ በተለይም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ለአፍሪካ ተናጋሪ ሆኖ በተጋበዘበት የታላላቅ መሪዎች ስብሰባ ላይ መገኘቱ ኢትዮጵያውያንን ሁሉ ሊያኮራ የሚገባው ነገር ነበር፤ ቢመቸን የሚያኮራን ነበር፤ መኩራቱ ሳይሆንልን ቢቀርም የማናፍርበት በሆነ መልካም ነበር፤ ምስጋናና ከንቱ ውዳሴ እንደጠበል በሚረጭበት ትልቅ ዓለም-አቀፍ ስብሰባ ላይ ዘለፋና ነቀፌታ መስማት አንገትን ያስደፋል፤ ነገር ግን ከመለስ ዜናዊ ጋር ኢትዮጵያ በዚያ ስብሰባ ላይ አንገትዋን አልደፋችም?
በግድም ይሁን በውድ አንድ መሪ አንድ ሕዝብ አናት ላይ ከተቀመጠ፣ ብዙ ነገሮች ያያዝዋቸዋል፤ ከነዚህ ነገሮች አንዱ ክብር-- ወይም ውርደት ነው፤ ሕዝብ ተዋርዶ መሪው ክብር አያገኝም፤ መሪው ተዋርዶ ሕዝብ ክብር አያገኝም፤ የአንዱ ውርደት ለሌላው ክብር ሊሆን አይችልም፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በስብሰባው ላይ የተጋበዘው ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካን አህጉርንም ወክሎ ነበር፤ በዚህ ሁኔታ ክብር ቢያገኝ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን አፍሪካን በሙሉም ያስከብር ነበር፤ ስለዚህም የዜና ማሰራጫዎች ሁሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ሲያወድሱ ኢትዮጵያም አፍሪካም አብረው ይወደሱ ነበር፤ አሁን ግን አንገቱን ስለደፋው ሰው ሲናገሩ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር እያሉ ነው፤ ያኔ እኛም አንገታችንን ባንደፋም ወደግብዣው ቋጥረነው የገባነው ትንሽ ክብር ይደፋብንና ውርደቱ ይሰማናል፤ የሚገዙትን ሕዝብ ሳያከብሩ ማስክበር ያስቸግራል፤ የሚገዙትን ሕዝብ ሳያከብሩ መከበርም ያስቸግራል፤ መሪና ሕዝብ ክብርንና ውርደትን ይወራረሳሉ።
በሃያ ዓመት የመሪነት ቦታ ተቀምጦ አንገቱን ቀና አድርጎ በኩራት የሚወረወርበትን ጉድፍ ሁሉ ለመቀበል የሚችልበትን፣ የሚናገርበት ብቻ ሳይሆን አንገቱን ሳይደፋ ለማዳመጥ የሚችልበትን መድረክ ሳያዘጋጅ በመቅረቱ የደረሰበት ውጤት በዓለም አቀፍ ስብሰባ ላይ አንገት መድፋት ነው።
በስንቱ ነገር ነው አንገታችንን የምንደፋው? በደሀነትና በችጋር፣ በመረጃ ማነቆ፣ በቴሌቪዥን እኛ የምንፈልገውንና የምንመርጠውን ለማየት አንችልም፤ በቴሌቪዥን ፕሮግራም እንኳ አጥፍቶ መጥፋት ሊባል ወደሚችል እልህ ውስጥ ገብተን ከዓለም ጋር ብቻ ሳይሆን ከእውቀት ጥበብ (ከቴክኖሎጂ) ጋር የምንታገል ይመስላል፤ ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ እየተባለ መራራ ኮሶ የሚጋቱበት ዘመን አክትሞአል፤ ዓለም በሙሉ ጎረቤት ሆኖአል፤ በአንዱ አገር ውስጥ የሚሆነው ውቅያኖስንና አህጉሮችን አቋርጦ ይሰማል፤ ይታወቃል፤ ከጎረቤቶቻችን ከአፍሪካ አገሮች ጋር በመረጃ ልውውጥ በጣም ዝቅተኛ ነን፤ በቴሌቪዥን ብቻ ሳይሆን በኢንተርኔት አገልግሎት ችግር ፍዳችንን እየበላን ነው።
ለዚህ ነው አንገታችንን የምንደፋው፤ አንገታችንን ስንደፋ ክብራችን ይፈስብንና ገበናችን ይጋለጣል፤ መከባበሩ የሚበጀው ለዚህ ነው።

Comments

እግዜር ይስጥልኝ ክቡር ፕሮፌሰር። መናናቅ እና አለማተማማን የኛ በሽታወች ናቸው ከዚህ ሳንፈወስ ፖለቲችካችን አይሰለጥንም

I have an "ethiopian" respect for prof. mesfin for his long standing acadamic contributions; but some times i got him trapped dwelling in self deceptitive justifications .so it is better for him to stop writing such kind of worth less pieces and concentrate in his prayer.

ፕሮፌሰር መስፍን ባሉት እስማማለሁ። ውርደቱ ለጠ/ሚ መለስ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያና ለሕዝቦቿ ጭምር ነው። የጋዜጠኛ አበበም አድራጎት የብሶቱን መጠን ይገልጻል። የተሰደደበትን ምክንያት ያውቃል፤ በገዛ አገሩ ድምፁን መነጠቁ ያስከተለበትን ምሬት ያውቃል። በፕሮፌሰር አሳብ ላይ የምጨምረው አለኝ። በ1928 አፄ ኃይለ ሥላሴ በተባበሩት መንግሥታት ንግግር ሲያደርጉ የፋሺስቶች ጩኸት አንገት ያላስደፋቸው ምክንያቱ የኢትዮጵያን ሕዝብ ወክለው፣ እውነትን ይዘው በአምላክና በዓለም ሕዝብ ፊት ፍትሕ ይጠየቁ ስለነበረ ነው። እንዲያውም በሚያስፈራና በሚያኮራ ግርማ ነበር የቆሙት። ሊያሳፍሯቸው የመጡ ይልቅ አፈሩበት። ንጉሡ አጀማመራቸው መልካም እንደነበረ አንርሳ። የፕሬዚዳንት ኢሳይያስ እንኳ እዚህ ሊጠቀስም አይገባም። ያኔም ሆነ ዛሬ ከኤርትራውያን የሚታየው እያዩ እውነቱን መካድ ነው። ፈረንጆች "ግሩፕ ቲንክ" የሚሉት ነው። እና፣ ከኢትዮጵያ ሁናቴ ጋር ብዙ ማነጻጸር አይቻልም። አንድ የሚያመሳስለን ነገር ቢኖር ኢሳይያስና መለስ ሁለቱም በሕዝብ ምርጫ ሳይሆን በነበረው የሽግግር ሁናቴ ሥልጣን የያዙ መሆናቸው ነው። መለስ ግልጽ እንዳደረጉልን ከርሳቸውና ከፓርቲአቸው ወይም እርሳቸው ከሚሾሙት ውጭ ምርጫ እንደሌለን ነው። ሌላ የሚገርመው፣ በጥር ወር በተመረቀው የአፍሪካ ኅብረት ማእከል አፄ ኃይለ ሥላሴ ለአፍሪካ ስላበረከቱት አስተዋጽዖ መታሰቢያ እንዳያገኙ በጽኑ የተከራከሩት ጠ/ሚ መለስ ናቸው። አፍሪካውያን ግር እስከሚላቸው ድረስ ንጉሡን አንቋሸሿቸው፤ ክብር እንዲነፈጋቸው በጣም ታገሉ። የንጉሡ መከበር የሁላችንም [መለስን ጨምሮ] ክብር ሊሆን ሲችል። መለስ፣ እኛንም በሕዝብና በአገር ደረጃ ክብር ነሡን። ታሪክ ግን የ1928ቱን በደል እንደካሰን ሁሉ ወደፊት ጠ/ሚ መለስ በሌሉበት በሌላ ትውልድ ይክሰናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። መለስ ይህን ባደረጉ በጥቂት ወራት ውስጥ የዓለም መሪዎች በተገኙበት በርሳቸው ላይ መድረሱ እጅግ የሚገርም ነው፤ የሚያስፈራም ነው። ልብ ላለው ልብ የሚያስገዛ ነው።

Proff. keep your critics like this.I am learning a lot from you.

ewnet lemawrat lerso yeneberegn neger yhen yahl neber...eyader gen tsehofochoten saneb kemasebot yemileyu sew meselugn....ebakwon yhen yetesfa demtsoten ayatfuben??? be'komata bet 1 tat berk nat ena!(ke'megareja jerba bihonem) egzer yakoyot.

Good point.Long live prof

Egzeabher edmna tena yestot yethiopia tinsaye lmayet yabkawot

EGZABHER YBARKOT YETHIOPIAN TENSAYE LMAYET YABKAWOT

EGZABHER YBRKOT EDMNA TENA YESTOT YETHIOPIAN TENSAY LMYET YEBKAWT

This is a very good observation, but the analogy with Etitrea vis-s-vis Esayeyas is out of place. Both leaders are out of reach to their respective people.

İ AGREE WİTH THE WRİTER.WHY MELESE İS BOWİNG DOWN İS JUST HE İS ILLEGITIMATE TO RULE THE COUNTRY ANY MORE AND THİS WAS EXPOSED TO THE WORLD AT THE CONFERENCE İN US AS İT WAS LONG BEFORE EXPOSED TO ETHİOPİANS, İF NOT OPENLY EXPRESSED DUE TO FEAR EVERYONE KNOWS İNCLUDİNG MELES AND AZEB

I agree with Prof. Mesfin. He forwarded what he has thought right! Nothing else! Somebody who thinks about other human being's right to speak, write, express himself, move and live wherever he fits around his natural boundaries should act according to demands that come from the above-mentioned inalienable rights of an individual! Systematically or in dictatorial or in authoritarianism way of governing will take someone not more than 40 years of insecurity and worst life of his leadership! We have seen in our time! Mr. Meles is not from Mars and different from others who were like him in many ways! Mastewal melkam new! Mr. Melese n besewinetachew yemitela manim yelem gin alawaqinetachiwn megemet beshita honobachewal! Gitirnet motin teshekimo endmehead new! Ewinetu wededikuachew yemilachwim agatamiwn biyagegn esu ergitegna negn yemejimeriyaw dula anshi new! Yeqirb wedajochachew yehninu beyebetachew lemiwedochaw eyaweru new!

So Let me give an advice to Mr. Meles! Just give up your power because there are so many Ethiopians who are capable and willing to try the ROAD! Thank you for your efforts which bring us here whatever the results are! Time is coming to see all doings of all! Think little about your private life with your family! Confession never brought defeat but life- almost unparalleled good news to all humankind!

ፕሮፌሰር ከርሶ የበለጠ የፖለቲካም ሆነ የሌላ እውቀት ይኖረኛል ብዬ ባላስብም እንዴት ያምባገነኖች መዋረድ የሕዝባችው መዋረድ ሊሆን እንደሚችል አይገባኝም ሕዝብ መርጦ ፈቅዶ ያላስቀመጠው መሪ ቢዋረድ ያውም በሥራው እንዴት የሕዝብ ውርደት ሊሆን ይችላል???

eg/her ergem edem setowot yezhchen HaGer nethnet endyayu enlemenalen. keber leresewo Yhune prof.

Abebe Gellaw yalewen bemulu ena ye Ato Melesen huneta ke U-TUBE lay down load tederego beteyaze flash lay guadegnaye setetogn ayechewalew:: anidanedem degageme ayewalew. gen yalegebagn neger ye Ato Meles medeneget enidet new ye egna medeneget yemihonew? ye Ato Meles aniget medefat enidet new ye egna aniget medefat yemihonew? bezih huneta ye dereg baleseletanat metaser ena ke hager meseded ye ethiopia hizeb metaser ena ke hager meseded lihon new? ere yemaymesasel neger new Pro. eyanetsatseru yalut. lelaw betam yegerem ye Isayas Afewrkin be america ke hizebu gara meweyayet enide mesale manisato new:: Isaiyas afewerki eko yeleyelet ambagenen new so enidet new ye hizeb cheger adamach tederego enide misale yemikerebew? siketel hunetaw yetekesetew be 1983 akababi bihon liyaseked yechelal neber gen bekerebu mederegu ababalon furesh yaderegewal. so ledemocracy netsetser ina Ghanan, Tanzanian, bitekemu yeteshale meselegn.

Professor Mesfin is an icon to ethiopian. He is consistnet in his critics. Thank you for being model to ethiopian. I dont want to be rational to Professor Mesfin even if i can try to be. What ever any body say to my stand i always want to follow him "blindly" sorry to say this. God may give you rejim edime.

Ye Ethiopian sebeawi mebetoch gubaeee (EHRW) beteraw sebesebaaa lay kesetute Ye fit le fit Yedeferet temeket jemero eseke merechaaa 1997 derese enam tesedejeeee USA esekalehu Esekahun derese Ye edemeee lekeeee Degafiwonaaa adenakiwoooo negne. edemeeee setote Behager bet tegegnecheee ye nesanet bealache lay ye ersone negegere esekesemaaaa le ethiopia ye democracy genebaataaa etagelalehu.

I have seen the full video of the G-8 conference and Meles downs his head not because of Abebe Gelaws speech. Eske meche new endih eyeteweshashen yemininorew? I was hopeful of this generation but we are also poisoned by the minds and political objectives of simple minded few individuals. Be ESAT yetekenebabere video kayachuh Meles Zenawi be Abebe nigigir angetun yedefa limeslachuh yichilal. You always say u r fighting for freedom but you censor all comments. It is really funny

You selectively post comments, only those ideas who are comfortable to you. So what is the difference between you and EPRDF? I am political scientist by profession and I want no one to censor my ideas but it is ridiculous to believe that even private press's in Ethiopia do the censorship. I am really sorry,

Joro yalew yesema

only those ideas are comfortable tank you

Thank u prof. for ur comment and i agree with it. But does he really represent Ethiopia and the Ethiopian people? egnan yemaywokil ´meri´ tebiye biwared wurdetu lehager yemihon endet new? Esun yegabezut sewoch yiferu enji

thanks so much prof

Thank you professor you are the one and the only who give us food of peace!!!

Add new comment

Filtered HTML

  • Web page addresses and e-mail addresses turn into links automatically.
  • Allowed HTML tags: <a> <em> <strong> <cite> <blockquote> <code> <ul> <ol> <li> <dl> <dt> <dd>
  • Lines and paragraphs break automatically.

Plain text

  • No HTML tags allowed.
  • Web page addresses and e-mail addresses turn into links automatically.
  • Lines and paragraphs break automatically.