Add new comment
የተከበሩ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደባሪያም:
እርሶ መረጃ አለኝ ባሉበት ነገርላይ አስተያየት መስጠት እጅግ አላዋቂነት ስለሚሆን ዝምታ ጥሩ ነዉ:: ሆኖም ግን አንዳንዴ ስሜታዊ በመሆን የሚሰጡቸው ግምታዊ አስተያየቶች የሚናገሯቸዉ ትልልቅ ቁምነግሮችን ለመስማት እንቅፍት የሚሆኑ ይመስለኛል:: እርሶ የሚወዱት መጻፍ(መጻሀፍ ቅዱስ ማለቴን ነው) ጥቂት ዝንቦች መልካሙን የወይን ጠጅ ያገሙታል ነዉ የሚለዉ? አቶ ሲሳይ መጻፋቸው ላይ የቅንጅት መፈረካከስ በተመለከት ያነሱት መንም ነገር አላነበብኩም:: የመጽሀፉም ፈይዳ እኔ እስከገባኝ ድረስ ኢትዮጵያ ዉስጥ የነበረዉን የፍርድ ስረአት በዚያን ጊዜ ምን ይመስል እንደነበር ማስገንዘብ እንጂ ቅንጅት ዉስጥ የነበረዉን የፖለቲካ ሽኩቻ ማቅረብ አለመሰለኝም:: እርግጥ ነዉ አቶ ልደቱ ባደባባይ የናገራቸዉ የነበሩ ነገሮች ለፍርድቤት የማስረጃ ግብአትነት መዋላቸዉ በተመለከት ጥቂት ብሏል ያግን እርሶ ነበረ የሚሉትን የስልጣን ሽኩቻ በተመለከተ አይደለም::

Tsnat Bekalu (not verified)
Tue, 05/22/2012 - 01:54
Permalink