Add new comment
ጠላታችን በሚል ርዕስ መጻፉ አልተመቸኝም።
ጠላታችን በሚል ርዕስ መጻፉ አልተመቸኝም። የዚያ ዘመንም ሆነ ያአሁኑ መሪዎች ቢያጠፉም ጠላት የሚል ቃል ተጠቅሞ መጻፉ ያስከፋል።ይህ በኢትዮጵያ ወጣቶች አዕምሮ የሚፈጥረዉ መንፈስ መልካም የሚሆን አይመስለኝም።እርግጥ ነዉ ኢህአዴግ ስልጣኑን ለረጅም ጊዜ ለማቆያት በሚል ግልጽ አላማ ልዩነታችንን በብዙ እጥፍ አብዝቶታል። ብዙ ከፋፍሎናል።ህዝቡ እርስ በርሱ እንዲጠላለፍ ተደርጉዋል። ነገር ግን እኛ ኢትዮጵያዊያን ዘር ሀይማኖት ሳይገድበን ለብዙ ዘመናት በደም በስጋ የተሳሰረ የጋራ ማንነትን ገንብተናል። ይህ እዉነታ መሪ በተቀያየረ ቁጥር እንደማይለወጥ ለዘመናት ባሳለፍናቸዉና ኢህአዴግ እንዲከር ባደረገብን ፈተናዎች ተፈትነን አልፈነዋል።አሁን ያለዉ ያዘረኝነት ፈተናም የከፋ ነዉ።እዉነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ጠላታችን እያሉ መጻፉን አልወደድኩትም። ፍቅር ያሸንፋል!

በረከት መሀመድ (not verified)
Fri, 06/22/2012 - 21:44
Permalink